....ጤቅላ በእስር ቤት ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በተገች ጊዜ ቅዱስ ጳውሎስን ከከተማው ቅጥር ውጭ አውጥተው እንዲጥሉት በእሳትም እንዲያቃጥሉት አዘዘ፤እሳቱ ግን በቅዱስ ጳውሎስ ላይ አንዳች ነገር ማድረግ አልቻለም።ጤቅላም ለፍርድ ቀረበች፤በእሳትም ተቃጥላ በቲያትር አደባባይ እንድትገደልና ለሴቶች ሁሉ መቀጣቻ እንደትሆን አዘዘ።....እጅና እግሯ ታስሮ እንጨትና ገለባ ወደተከመረበት ክምር ትገደል ዘንድ ቀረበች።ድንገተኛ ዝናብ ተነስቶ እሳቱንም አጠፋ።ገለባውንና እንጨቱን አራሰ።ቅድስት ጤቅካም ዳነች።
ቅድስት ጤቅላ ቅዱስ ጳውሎስ እስር ቤት በነበረበት ጊዜ ትምህርቱን ለመማር በሄደችበት ጊዜ የገጠማት ፈተና
....በእርሷ ላይ የተላለፈው ፍርድ አንዱ ሌላውን ተከትሎ የተፈጸመና ሌሎች ቅጣቶች ያሉበት ቢሆንም፤በእርሷ ላይ ኃይል ሳይኖረው ቀረ።ብዙ አዞዎችና ዓሳ የሚበሉ ፍጥረታት ወደ ነበሩበት ባህር ተወረወረች የጌታን ስም ጠርታ ዳነች።አንዳችም ጉዳት አላስከተሉባትም።
የሀገረ ገዥው በቅድስት ጤቅላ ላይ የወሰደው ፍርድ
...ስለምን ሕጉ እኛን የሚቆጣጠረው ሕግ እርሱም የሥጋ ሞትን ከቅጣቶች ሁሉ በላይ አስቀመጠው?
ከቅጣቶችም ሁሉ በላይ ሆኖም ስፍራ ተሰጦታል።ሞት ምንም እንዳልሆነ ልናስብ የሚገባን በየትኛው መንገድ ነው?
...የምኖንርበት ቤት የምንሰራው አእምሮአችን በሙቀትና በቅዝቃዜ ብዛት እንዳይገላታ አይደለምን?
...የዕለት እንጀራችንን ደክመን የምናገኝበት በሕይወት ለመኖር የምናደርገው ማንኛውም ጥረት በሞት ፍርሃት ውስጥ ተጠቃልሎ የተያዘ ነው።መድኃኒትስ ለሰው ልጆች ስለምን ተሰጠ?
ከመጽሃፉ የተወሰደ
ነፍስ ወደ ፈጣሪዋ በምታደርገው የነጻነት ጉዞ ራስን መካድ ከዓለም መለየት ፈቃድ ሥጋን ለፍቃደ ነፍስ ወደሚያስገዙት ስፍራ መጓዝን የሚጠይቅ መሆኑን፤በዚህ ሕይወት የተጓዙ ቅዱሳን ፍኖት ያስረዳል።
ከመጽሃፍጉ ተወሰደ
ሐመር መጽሔት
|